Posts

Showing posts from February, 2018

ለሀሰተኛ የማህበራዊ ድረ ገጽ አካውንቶች የህግ ማዕቀፍ ወይስ እገዳ

የዓለም አቀፉ የማህበራዊ ትስስር ድረ ገጽ የሆነው ፌስቡክ ካሉት ከሁለት ቢሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች መካከል በሐሰትና በማመሳሰል የተከፈቱት 270 ሚሊዮን መሆኑን ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። በኢትዮጵያም የፌስቡክ ተጠቃሚ ከሆኑት አራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ሰዎች መካከል በውሸትና በማስመሰል በባለስልጣናት፥ በታዋቂ ሰዎች እንዲሁም በተቋማት ስም የተከፈቱ አካውንቶች እንዳሉና አሉታዊ ተፅዕኖ እየፈጠሩ መሆኑ ይገለጻል። የማስመሰል አካውንት ከተከፈተባቸው መካከል ሻለቃ ሃይሌ ገብረስላሴ እንደሚለው፤ እርሱን በማስመሰል በተከፈተው አካውንት ላይ እንደሚተላለፈው መልዕክት ቢሆን ለህይወቱም ጭምር አስጊ ሁኔታ ይፈጠር ነበር። የብዙ ድርጅቶች ባለቤትና ሁለት ሺ ያህል ሰራተኞችን በስሩ የሚያስተዳድር ሲሆን፤ ይህም ጉዳት የእርሱ ብቻ ሳይሆን የበርካቶችም ጭምር መሆኑን ሊታወቅ ይገባል። የውሸት መልዕክት በእርሱ ስም ማስተላለፍም ትልቅ ወንጀል ነው። ችግሩን ለመፍታት ሲል ወደ ተለያዩ ተቋማት መንቀሳቀሱን የጠቀሰው ሻለቃ ሃይሌ፤ ወደ ፖሊስ ባቀናበት ወቅት ህግ ነውና « የምትጠረጥረው ሰው አለ ?» ወደ ፍርድ ቤት ሲሄድ ደግሞ « የተጨበጠ ነገር አለ ?» መባሉ ጉዳዩን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማዘጋት እንዳይችል አድርጎታል። በውሸት ከተነገሩበት መካከል በጣም የረበሸው በተለይ በሶማሌና በኦሮሚያ ክልል መካከል በተከሰተው ሁኔታ ኦሮሚያን ወግኖ እንደቆመ ተደርጎ መነገሩ በሌላው ወገን ሊጠላ የሚያስችለው ከመሆኑም በላይ በህይወቱ ላይም አደጋ ሊያስከትልበት ይችል እንደነበር ነው የተናገረው። እርሱ እንደሚናገረው፤ እንዲህ አይነቱ ወንጀል በኢትዮጵያ ወንጀለኛ መቅጫ ህግ አልተካተተም። ስለዚህ ራሱን የቻለ ህግ ሊቀረፅ ይገባል። ወንጀሉ ከባድ መሆኑን የሚያውቀው ደግ...

ፓርላማው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ላይ እንዲወስን በአስቸኳይ ተጠራ

Image
    የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በአስቸኳይ አዋጁ ላይ እንዲወስኑ ለአስቸኳይ ስብሰባ ተጠሩ፡፡ ከየካቲት 1 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ለአንድ ወር ዕረፍት የወጡት የፓርላማ አባላት ለአስቸኳይ ስብሰባ በመጠራታቸው ምክንያት፣ ከማክሰኞ የካቲት 20 ቀን 2010 ጠዋት ጀምሮ ሪፖርት ሲያደርጉ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ የፓርላማው አባላቱ የተጠሩት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የካቲት 9 ቀን 2010 ዓ.ም. ያፀደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ ተወያይተው ለመወሰን መሆኑን፣ የተገኙ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ ተግባራዊ የማድረግ ሥልጣን በሕገ መንግሥቱ ቢሰጠውም፣ ፓርላማው በሥራ ላይ በሚገኝበት ጊዜ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በ48 ሰዓት ውስጥ አቅርቦ ማፀደቅ ይኖርበታል፡፡ ፓርላማው በሥራ ላይ በማይገኝበት ጊዜ ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በ15 ቀናት ውስጥ አቅርቦ ማፀደቅ ይኖርበታል፡፡ ፓርላማው ለዕረፍት በተበተነበት ወቅት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አሥራ አምስተኛ ቀኑን የሚይዘው በመጪው ዓርብ የካቲት 23 ቀን 2010 ዓ.ም. በመሆኑ በዛው ዕለት ተሰብስቦ እንዲወስን፣ አባላቱ በአስቸኳይ ከዕረፍት እንዲመለሱ በአፈ ጉባዔው አማካይነት ተጠርተዋል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በሥራ ላይ ቢውልም በተወሰኑ የኦሮሚያና የአማራ ክልል አካባቢዎች ሰላማዊ ተቃውሞዎች ሲካሄዱ ተስተውሏል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን እንዳያፀድቁ በማኅበራዊ ድረ ገጾች ጥሪ እየቀረበላቸው መሆኑን መገንዘብ ተችሏል፡፡ ይህንን ሁኔታ ያስተዋለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኮማንድ ፖስት ሴክሬታሪያት ማክሰኞ የካቲት 20 ቀን 2010 ባ...

N Korea 'providing materials to Syria chemical weapons factories'

North Korea has been sending equipment to Syria that could be used to make chemical weapons, a UN report says. Some 40 previously unreported shipments were made between 2012 and 2017, the report found. Materials included acid-resistant tiles, valves and pipes. The report - yet to be released - said N Korean missile specialists had been seen at Syrian weapon-making centres. The allegations follow new reports of chlorine being used by Syrian forces, which the government denies. A second daily pause in fighting in the Eastern Ghouta region outside Damascus is due to begin, to allow in relief aid. Aid was unable to enter the rebel-held region on Tuesday - the first of the five-hour "pauses" in fighting - after clashes continued. Activists blamed government air and artillery strikes, while Russia said rebels had shelled a "humanitarian corridor" meant to let civilians leave. What are the allegations against North Korea? North Korea is under international...